የብፁዕ አባታችን የአቡነ መልከ ጼዴቅ ፪ኛ ዓመት የዕረፍት መታሠቢያ ቀን ነገ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም በመላው ኢትዮጵያ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በጸሎተ ፍትሐትና በቅዳሴ ታስቦ ይውላል። በይበልጥ ደግሞ በምሑር ኢየሱስ ገዳም ብዙ የመንፈስ ልጆቻቸው፣ አረጋውያን መነኮሳትና ተማሪዎች አስበዋቸው ይውላሉ። የተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተስቦች አሁንም ቢሆን በመላው ዓለም የምትገኙ ሁላችሁም የብፁዕ አባታችን በርካታ ሥራዎችን ዳር ለማድረስ በምትችሉት ሁሉ እንድትራዱ እናሳስባለን። እግዚአብሔር አምላክ ደጋግ አባቶችን ያብዛልን፤ የብፁዕ አባታችን ነፍስ በገነት መንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን።

This entry was posted in Uncategorized. Bookmark the permalink.