አቡነ መልከ ጼዴቅ ያረፉበት አንደኛ ዓመት መታሠቢያ ቀን ታስቦ ዋለ

ነገ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፫ ዓ/ም ብፁዕ አባታችን ያረፉበት አንደኛ ዓመት መታሠቢያ ቀን ነው። በመላው ኢትዮጵያ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በጸሎተ ፍትሐትና በቅዳሴ ታስበው ይውላሉ። በይበልጥ ደግሞ በምሑር ኢየሱስ ገዳም ብዙ የመንፈስ ልጆቻቸው፣ አረጋውያን መነኮሳትና ተማሪዎች አስበዋቸው ይውላሉ። አምላካችን እግዚአብሔር የብፁዕ አባታችንን ነፍስ በገነት መንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን አሜን።

This entry was posted in Uncategorized. Bookmark the permalink.