የዝክረ አቡነ መልከ ጼዴቅ ኮሚቴ ገቢው ብጹዕነታቸው ለሰበሰቧቸው ልጆች ማሳደጊያ እና ለጀመሯቸው ሥራዎች ማስፈጸሚያ የሚሆን ተንቦላ እያከፋፈለ ይገኛል። እጣው በጥቅምት ወር እንደሚወጣ የተገለጸው ተንቦላን በየእስቴቱ ለማከፋፈል በጉ ፈቃደኛ የሚሆኑ የብጹዕነታቸውን ወዳጆች ጥሪ እያቀረበ እንደሚገኝ የገለጸ ሲሆን ፈቃደኛ የሆኑ ግለሰቦች በ 202-656-ZAMT / 202-656-9268 በመደወል ኮሚቴውን ማነጋገር እንደሚችሉ ገልጻል። በተያያዘ ዜናም በአንድ አንድ ኢትዮጵያዊያን በሚበዙበት የአሜሪካ ግዛቶች በዲሲ እንደተደረገው አይነት የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ለማዘጋጀት እያሰቡ ያሉ ምዕመናን እንዳሉ የተገለገ ሲሆን ለዚህ ዝግጅት ማስተባበር ፈቃደኛ የሆኑ ካህናት አባቶች ሰንበት ተማሪዎች እና ምዕመናን በንዑስ ኮሚቴ ለማደራጀት ይቻል ዘንድ ከላይ በተገለጸው ስልክ በመደወል ኮሚቴውን ማነጋገር የሚቻል መሆኑን አሳስበዋል።
-
What is new?
-
Recent Posts